የሌሊት አገልጋዮች በቤተ መቅደስ ጌታን እንዲመሰግኑ ጥሪ

1

እነሆ፥ እናንተ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሁሉ፣ በሌሊት በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ የምትቆሙ፣ እግዚአብሔርን ባርኩ።

2

በመቅደስ እጆቻችሁን አንሡ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ።

ከጽዮን በረከት በአዳም ላይ ይታወቅ

3

ሰማይንና ምድርን የፈጠረ እግዚአብሔር ከጽዮን ይባርክህ።